የ2014 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል አከባበር እና የቅዱሳን መካናት መንፈሳዊ ጉብኝት
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሃዱ አምላክ አሜን በቅድስት ሀገር እየሩስሳሌም አማን ኢትዮጲጲያ እሰጎብኚ እና የጉዞ ወኪል ድርጅት የ2014 ዓ.ም የትንሣኤ በዓል አከባበር እና የቅዱሳን መካናት መንፈሳዊ ጉብኝት ዝርዝር መርሃ ግብር፡፡ 1.ሚያዚያ 14/2014 ዓ.ም ረቡዕ(April 20 2022) በቅድስት ሀገር እየሩሳሌም የትንሣዔን በዓል ለማክበር ከኢትዮጲያ የሚመጡ አትዮጲያዊ ምዕመናን በእስራኤል አለማቀፋዊ አውሮፕላን ማረፊያ( ቤን ጎሪዮን የአውሮፕላን ጣቢያ) በመገኘት በቬርድ ሃሻሮን የጉዞ ወኪል ተወካይ ለእንግዶቹ ወደ ቅድስት ሃገር የእንኳን ደህና መጣችሁ አቀበባል ይደረጋል፡፡ እንግዶቹም በተዘጋጀላቸው አውቶበስ ሁነው ወደ እየሩሳሌም ይጓዛሉ በተያዘላቸውም ሆቴል እረፍት…

